15.5 C
Addis Ababa
October 3, 2023
Local News

በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ጥሬ እቃ ስም በ8 ኮንቴነር የታሸገ ያለቀለት የኤሌክትሮኒክስ እቃና አልባሳት ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ሲል በሞጆ ደረቅ ወደብ ተያዘ

በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ጥሬ እቃ ስም በስምንት ኮንቴነር የታሸገ ያለቀለት የኤሌክትሮኒክስ እቃና አልባሳት ወደ ሃገር ውስጥ ሊገባ ሲል መያዙን የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን አስታወቀ።

በባለስልጣኑ የሞጆ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የጉምሩክ ስነ-ስርዓት የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ግርማ በንቲ እንደገለጹት እቃው የተያዘው ተመሳስሎ ሊያልፍ ሲል በሞጆ ደረቅ ወደብ ላይ ነው።

በአምስቱ ኮንቴነሮች የተያዘው ለጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሚውል ብትን ጨርቅ እንደሆነ ተመስክሮለት በጁቡቲ ወደብ የገባ ቢሆንም በተደረገ ፍተሻ ከምርት ጋር ተመሳስሎ የታሸገ 410 ቦንዳ ያለቀለት አዳዲስ አልባሳት ሆኖ ተገኝቷል።

ከተያዙት አልባሳት መካከልም ያለቀለትና ለገበያ ሊበተን የሚችል በርካታ ዘመናዊ ጃኬትና ሱሪ እንደሚገኝበት ጠቅሰዋል።

በሶስቱ ኮንቴነሮች የተያዘው ደግሞ ለፋብሪካ በጥሬ እቃነት የሚውል የክር ማግ መሆኑን ተመስክሮለት ወደ ሀገር ውሰጥ እንዳይገባ የተከለከለ የኤሌክትሮኒክስ እቃ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኤሌክትሮኒከስ እቃው በ1 ሺህ 500 ካርቶን የታሽገ በለ 200 ዋት 75 ሺህ አምፖል መሆኑንም አመልክተዋል።

“ይህ ምርት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አባካኝ መሆኑ በሚመለከተው የመንግስት አካል የተረጋገጠ በመሆኑ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለ ነው” ብለዋል።

የንብረቱ የዋጋ ግምት እየተሰላ መሆኑን ገልጸው ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ እንዲጣራ ለጉምሩክ ህግ ማስከበርና ምርመራ ክፍል መተላለፉን አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

Related posts

An Updated Approach to Addressing Foreign Exchange Supply Challenges in the Manufacturing Industry

Areda Batu

Bahir Dar University Opened an Exhibition for the University Community on June 5, 2023, Showing 60 years of Journey.

Areda Batu

Ethiopian Textile and Apparel Professional Association Founded

Areda Batu

This website uses cookies to improve your experience. We'll assume you're ok with this, but you can opt-out if you wish. Accept Read More

Privacy & Cookies Policy
Show Buttons
Hide Buttons